05 Jul
05Jul

የቀድሞው የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ሰዓረ መኮንን ህይወታቸው ከማለፉ ከሰዓታት በፊት ከአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ኢንጂነር ታከለ ኡማ ጋር ችግኝ በተከሉበት ቦሌ ሩዋንዳ አካባቢ የመታሰቢያ ፓርክ ሊሰራላቸው ነው፡፡

በመታሰቢያ ፓርኩ ውስጥ የጀኔራሉን ክብር በሚመጥን መልኩ የማስታወሻ ሀውልት እንደሚሰራላቸው የከንቲባ ፅህፈት ቤት አስታውቋል።

ችግኙን ከተከሉበት ከቦሌ ሩዋንዳ ጀምሮ እስከ አትላስ ሆቴል ያለው ጎዳና በስማቸው እንዲሰየም የከተማ አስተዳደሩ ወስኗል፡፡

በከተማው የሚገኙ የስነ-ህንጻና የስነ-ጥበብ ትምህርት ቤት ባለሙያዎችም የጄኔራል ሰዓረን የማስታወሻ ሀውልት ንድፍ ሰርተው   ማጠናቀቃቸው ተገልጿል፡፡

Comments
* The email will not be published on the website.
I BUILT MY SITE FOR FREE USING