የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአድዋ ጀግኖችን ለመዘከር እና የታሪካዊ ድሉን ሁለንተናዊ ይዘት ለትውልድ ለማሻገር ሊገነባ የታሰበው የአድዋ ማዕከል በዛሬው ዕለት ግንባታው ተጀምሯል፡፡
የአድዋ ማዕከል ግንባታ ለረዥም ጊዜያት ሳይለማ በቆየው እና ከሚድሮክ ተመላሽ በተደረገው ቦታ ላይ የሚካሄድ ሲሆን የግንባታው ወጪ ሙሉ በሙሉ በከተማ አስተዳደሩ የሚሸፈን ይሆናል፡፡
China Jiangsu International E.T.C.C በተባለ አለም አቀፍ ኩባኒያ ግንባታው የሚካሄደው የአድዋ ማዕከል በሁለት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ግንባታውን በማጠናቀቅ ለህዝብ አገልግሎት ክፍት የሚደረግ ይሆናል፡፡
የማዕከሉ ግንባታ ሲጠናቀቅ በውስጡ "ሁሉም ከዚህ ይጀምራል!" የሚል የአዲስ አበባ ከተማ 'ዜሮ(0.00) ኪ.ሜ' ምልክት ያርፍበታል፡፡
(ከንቲባ ጽ/ቤት)